loading
የቦክሲንግ ዴይ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

የቦክሲንግ ዴይ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

አርትስ ስፖርት 17/04/2011

የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ 19ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መርሃግብር (BOXING DAY MATCHES)፡ ዛሬ ዘጠኝ ያህል ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

ከቀኑ 9፡30 በክራቨን ኮቴጅ ፉልሃም ከ ወልቭስ ይጫወታሉ፤ ምሽት 12፡00 ላይ በተመሳሳይ ሰዓት በርከት ያሉ ግጥሚያዎች ሲከናወኑ፤ የሊጉ መሪ በአንፊልድ ሊቨርፑል ከ ኒውካስትል ዩናይትድ ይገናኛሉ፣ ማንችስተር ሲቲ ደግሞ ወደ ኪንግ ፓወር አቅንቶ ሌስተር ሲቲን ይገጥማል፤ አሰልጣኝ ኦሌ ጉናር ሶልሻዬር የኦልትራርድ የመጀመሪያ ጨዋታ በማንችስተር ዩናይትድ እና ሀደርስፊልድ መካከል ይከናወናል፣ በሴል ህረስት ፓርክ ክሪስታል ፓላስ ከ ካርዲፍ ሲቲ፣ በቱርፍ ሞር በርንሊ ከ ኢቨርተን፣ በዊምብሌ ደግሞ ቶተንሃም ከ በርንማውዝ ይፋለማሉ፡፡

ምሽት 2፡15 ሲል ብራይተን በአሜክስ አርሰናልን ይፈትናል፤ በቪካሬጅ ምሽት 4፡ 45 ዋትፎርድ ከ ቼልሲ ይገናኛሉ፡፡

በሊጉ ሀሙስ ምሽት 4፡45 በሴንት ሜሪ ሳውዛምፕተን ከ ዌስት ሃም ዩናይትድ ተጫውተው የሳምንቱ መርሃግብር ይጠናቀቃል፡፡

የደረጃ ሰንጠራዡን ሊቨርፑል በ48 ነጥብ ሲመራ፣ ማንችስተር ሲቲ በ44 ይከተላል፣ ቶተንሃም ሶስተኛ በ42፣ ቼልሲ እና አርሰናል በተመሳሳይ 37 ነጥብ አራተኛና አምስተኛ፤ ማንችስተር ዩናይትድ ደግሞ በ29 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *