loading
የአሚሶም ሽልማት ለኢትዮጵያ ወታደሮች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25 ፣ 2013 አሚሶም ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት አስተዋጽኦ ላበረከቱ የኢትዮጵያ ወታደሮች የክብር ሜዳልያ ሸለመ:: በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል (አሚሶም) ስር የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ላበረከቱት አስተዋጽኦ የክብር ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኑ፡፡ ሽልማቱ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች በሶማሊያ በነበራቸው የአንድ አመት ከስድስት ወር ቆይታ በሃገሪቱ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን በተደረገው ጥረት ላደረጉት አስተዋጽኦ እውቅና ለመስጠት ያለመ
መሆኑን አሚሶም አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያውያን ወታደሮቹ አልሸባብን ለመደምሰስ በተካሄደው ዘመቻ ከጂቡቲ እና ከሶማሊያ ወታደሮች ጋር በበለተወይኒ ሴክተር አራት ተሰማርተው ግዳጃቸው የተወጡ ናቸው፡፡በአሚሶም የጂቡቲ ጦር አዛዥ ኮሎኔል አብዲራህማን ሃሬድ፥ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች የሶማሊያን ደህንነት ለማስጠበቅ ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ አያይዘውም ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ጊዜ፣ ጉልበትና ህይወታቸውን ለሰጡ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ያላቸውን ክብር ገልጸዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *