loading
ዶ/ር መሃመድ ኢብራሂም ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር ተገናኙ

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ የሱዳንና እንግሊዝ ዜጋ የቢዝነስ መሪና የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን መስራች የሆኑትን ዶ/ር መሃመድ ኢብራሂም ዛሬ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። ሁለቱ ወገኖች ስለአስተዳደር፣ ስለ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትና በአፍሪካ እና በኢትዮጵያ ስላሉ ተያያዥ ችግሮች ተወያይተዋል። እንዲሁም ወሳኝ የሆነው አህጉራዊ የወጣቶች ተሳትፎና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ተወያይተዋል። ዶ/ር መሃመድ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ለውጥ በማድነቅ አንድነት ላይ ተመስርቶ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምኞታቸውን ገልፀዋል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *