loading
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ዩኤንዲፒ ተወካይ ጋር ተወያዩ

አርትስ 19/03/2011

 

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ከተወካዩ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የለውጥ ሂደት ላይ መምከራቸው ነው የተሰማው።

ፕሮግራሙ በዚህ የለውጥ ሂደት ላይ አስተዋጽዖ ማበርከት በሚችልባቸው መንገዶች ዙሪያ ጋር መነጋገራቸውም ተገልጿል፡፡

እንደ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ከተመድ የልማት ፕሮግራም ተወካይ በተጨማሪከሌሎች የስራ ኃላፊዎች ጋርም ተወያይተዋል፡፡

ፕሬዚዳንቷ በቀድሞው የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ ባንኪሙን እና በኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ከተቋቋመውየአየር ንብረት ኮሚሽን የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ማካሄዳቸውም ተነግሯል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *