loading
በቻይና ከኢቦላ ጋር የሚመሳሰል ቫይረስ መገኘቱ ተሰማ

በቻይና ከኢቦላ ጋር የሚመሳሰል ቫይረስ መገኘቱ ተሰማ

በቻይና ከኢቦላ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ቫይረስ በሌሊት ወፍ ላይ መገኘቱን ጆርናል ኔቸር ማይክሮ ባይሎጂ ላይ የተገኘ ጥናት አመለከተ።

ቫይረሱ “መንገላ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ከኢቦላ ጋር የሚስመሳሰል እና ሀይለኛ መሆኑን ነው ጥናቱ ያመለከተው፡፡
ቫይረሱ በቻይና ዩዋን ግዛት የሌሊት ወፍ ላይ ነው የተገኘው፡፡

ቫይረሱም በሰዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት እና ህመም  እንደሚያስከትል ያስነበበው ጥናቱ የሌሊት ወፎቹ ያሉበትን መልክአ ምደር ማጥናት ቫይረሱ ወረርሽኝ እንዳይሆን እና የሚያደርሰውን ጉዳት ቀድሞ ለመከላከል እንደሚያስችል አስቀማጧል፡፡

ተመራማሪዎቹ በቀጣይ በሚያከናውኑት ጥናት “መንገላ” ቫይረስ ወደ ሌሎች ዝርያዎች መተላለፍ ይችላል?፤ የሚተላለፍ ከሆነስ በምን መልኩ፤ የሚሉት ላይ እንደሚሰሩ ነው በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡

ቫይረሱ ሳይሰራጭ በፊት በጥናት መለየቱ በቻይና ከተሰሩ ጥናቶች ጠንካራው እንደሚያደርገው እየተነገረለት ነው፡፡

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *