loading
የአውሮፓ ፓርላማ በሚቀጥለው ሳምንት በዘረኝነት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት ላደርግ ነው አለ፡፡

የጥቁር አሜሪካዊውን ጆርጅ ፍሎይድን ግድያ ተከትሎ በርካታ ሀገራ እና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥው መወያያት ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡
ህብረቱ በጥቁሮች ላይ የሚደርሰው ጫና እንዲቆም የሚያደርግ አሰራር ለመዘርጋት እና የዘር መድሎ የሚያደርጉ ግለሰቦችና ቡደኖችን የሚያወግዝ ውይይት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዩሮ ኒውስ እንደዘገበው በአውሮፓ ህብረት ቁልፍ የሚባሉ ስራዎች የተያዙት ነጭ ቀለም ባላቸው ግለሰቦች ሲሆን ከተመሰረተ ከ60 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የአውሮፓ ኮሚሽን አንድም ጊዜ በጥቁር ተመርቶ አያውቅም፡፡
የኮሚሽኑ ፕዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሊየን በዚህ ውይይት እያንዳንዳችን በደመነፍስ ስናራምደው የነበረውን አድልዎ እንፈትሽበታለን ብለዋል፡፡
ፕሬዚዳንቷ ውይይቱን አስመልክተው ባደረጉት ንግግር ከእንግዲህ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ዘረኝነት የሚባል ነገር ቦታ አይኖረውም ሲሉ የማረጋገጫ ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡
ብላክ ላይቭስ ማተር የሚለው ዓለም አቀፍ ይዘትን የተላበሰው ተቃውሞ በዘር መድሎ የተገፉትን እና ፍትህን የሚሹትን አውሮፓዊያን ሁሉ አነቃንቋል ያሉት ኮሚሽነሯ ለዚህም አጥጋቢ ምላሽ ለመስጠት ጊዜው አሁን ነው ብለዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *