loading
ጆን ኦቢ ሚኬል በድጋሜ ወደ ንስሮቹ ተመልሷል

 

የዘንድሮውን የውድድር ዓመት በእንግሊዙ ሚድልስብራ ያሳለፈው ናይጀሪያዊው አማካይ ከ2018 የሩሲያ የዓለም ዋንጫ ውድድር በኋላ ከናይጀሪያ ብሔራዊ ቡድን ጋር የተለየ ሲሆን አሁን ወደ ንስሮቹ ስብስብ በድጋሜ መመለሱን አስታውቋል፡፡

አምበሉ ሚኬል ከንስሮቹ ጋር የመጨረሻውን ጨዋታ በዓለም ዋንጫው ከአርጀንቲና ጋር ካደረገ በኋላ፤ ብሔራዊ ቡድኑ ባደረጋቸው ሰባት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ እና ሌሎች ግጥሚያዎች ላይ አልተሳተፈም፡፡

ሚኬል አሁን ሙሉ ትኩረቱን ከሀገሩ ጋር በማድረግ አራተኛ ዋንጫውን ለማሳካት እንዳለመ ጎል ዶት ኮም አስነብቧል፡፡

የናይጀሪያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫው በምድብ ለ ከማዳጋስካር፣ ቡሩንዲ እና ጊኒ ጋር ተደልድላለች፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *