loading
ሊቨርፑል ለማንችስተር ሲቲ እጅ ሰጥቷል

ሊቨርፑል ለማንችስተር ሲቲ እጅ ሰጥቷል

ቀያዬቹ ያለመሸነፍ ጉዟቸው በሲቲ ተገትቷል

ተጠባቂው የ21ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ በማንችስተር ሲቲ እና ሊቨርፑል መካከል ተካሄዶ ባለሜዳዉ ቡድን ሲቲ የ 2 ለ 1ጣፋጭ ድል አስመዝግቧል ።

የማ.ሲቲን ጎሎች ኩን አጉዌሮ እና ሊሮይ ሳኔ ሲያስቆጥሩ፤ ሮቤርቶ ፊርሚኖ የቀያዮቹን ከሽንፈት ያልታደገች ጎል ከመረብ አዋህዷል ።

በየርገን ክሎፕ የሚመራው የመርሲ ሳይዱ ቡድን ፤ ለ20 የሊጉ ጨዋታዎች ያህል አስቀጥሎት የነበረውን ያለመሸነፍ ግስጋሴ በመጨረሻ በፔፕ ጓርዲዮላ ቡድን ተገትቷል ። እስከዚህ ሽንፈት ድረስ ሊቨርፑል በሊጉ ያልተረታ ብቸኛው ቡድን ነበር ።

የሊቨርፑልን ሽንፈት ተከትሎ በሁለቱ ቡድኖች መካከል ያለው የነጥብ ልዩነት ከሰባት ወደ አራት ዝቅ ብሏል ።

ሊጉን ሊቨርፑል በ54 ነጥብ ሲመራ ፤ ሲቲ በ50 ይከተላል ፤ ቶተንሃም በ48 ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *