loading
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሜሪካ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ግንቡን እናፍርስ ድልድዩንም እንገንባ” በሚል መሪ ቃል በአሜሪካ በሚያደርጉት ቆይታ ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይታደማሉ ተባለ፡፡
በዋሽንግተንዲሲ፣ በሎሳንጀለስና በሚኔሶታ በሚካሄዱ የድጋፍ ሰልፎችም የተለያዩ ፕሮግራሞች ተዘጋጅተዋል፡፡
በዋሽንግተን ዲሲ በሚደረገዉ የድጋፍ ሰልፍ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊና ትዉልደ ኢትዮጵያዊ የሚሳተፍበት ሲሆን ፤በሎሳንጀለስ ደግሞ የጥያቄና መለስ የዉይይት መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡
በሚኔሶታ በሚደረገዉ ሶስተኛዉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቆይታ የተለያዩ ፖለቲካዊ አመለካከት ያላቸዉ ግለሰቦችና ፖለቲከኞች የሚታደሙበት እንደሆነ ሰምተናል፡፡
የድጋፍ ሰልፉ አሜሪካ በሚገኘዉ የኢትዮጵ ያ ኤምባሲ የተዘጋጀ ሲሆን ፤ዶክተር አብይም በሁሉም ግዛቶች በሚያደርጓቸዉ ንግግሮች ኢትዮጵያ ሀገሩን የሚወድ ሁሉ ባለዉ ነገር ሀገሩን እንዲጠቅም ጥሪ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *