loading
ማይክ ፖምፒዮ የኢራንን መሪዎች ከማፊያ ጋር አመሳስለዋቸዋል

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማይክ ፖምፒዮ የኢራን መሪዎች ከመንግስትነት ይልቅ የማፊያ ባህርይ ጎልቶ ይንጸባረቅባቸዋል ብለዋል፡፡

ሮይተርስ እንደዘገበው ፖምፒዮ ለዚህ አባባላቸው በሀገሪቱ ያለውን ሰፊ ሀብትና የመሪዎቹን በሙስና መዘፈቅ በማሳያነት አቅርበዋል፡፡

ፖምፒዮ ካሊፎርኒያ ውስጥ ባደረጉት ቅስቀሳ የሚመስል ንግግር ኢራናውያን የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ ራሳቸው መወሰን አለባቸው፤ እኛ አሜሪካውያንም ከጎናቸው እንቆማለን ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በየፊናቸው አንዱ ሌላውን አታስፈራሩን ካልሆነ የከፋ እርምጃ እንወስዳለን የሚል የማሰፈራሪያ ዛቻ እያሰሙ ይገኛሉ፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *