loading
የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና እስከ ሐምሌ 25 ባለዉ ግዜ ዉስጥ ይፋ ይሆናል

የሐገር አቀፍ ትምህርት ፈተናዎች እና ምዘና ኤጀንሲ በስሜ በሀሰት የተከፈቱ የተለያዩ የፌስ ቡክ ፔጆች የ12ኛ ክፍል ፈተና ወጥቷል፡፡ በሚል ያስወሩት ወሬ ሀሰት ነዉ ብሏል፡፡ ኤጀንሲዉ አስከ ሀምሌ 25 ግን የፈተናዉ ዉጤት ይፋ እንደሚሆን ለአርትስ ቲቪ ተናግሯል፡፡
በኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ረዲ ሾና ለጣቢያችን ፈተናዉ ገና በእርማት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሀገር አቀፍ ትምህርት ፈተናዎች እና ምዘና ኤጀንሲ ትክክለኛዉ የፌስቡክ ገጽ 79 ሺ ተከታዮችና 78 ሺ ላይክ ያለዉ ሲሆን፤ የኤጀንሲዉን ሙሉ ስም www.neaea.gov.et በመጻፍ ወደ ድረ ገፁ በመግባት መረጃዎችን ማግኘት ይቻላል ብለዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *