![](http://artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/6971F5FD-B173-4D80-9321-C3CC72157BB1.jpeg)
በሀዋሳ የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖቻችን ከዛሬ ጀምሮ ወደ ቀያቸው ይመለሳሉ፡፡
የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት በሀዋሳ በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች ከ 1 ወር በላይ የቆዩ ተፈናቃዮች ከዛሬ ጀምሮ ወደ የቀያቸዉ ይመለሳሉ ብለዋል፡፡
አቶ ሚሊዩን ተፈናቃዮቹ የሚመለሱባቸዉ መንደሮች የቀድሞ ሰላማቸዉን ማግኘታቸዉን ተናግረዋል፡፡
ተፈናቃዮቹ እስኪቋቋሙ ድረስ ቤተሰብ ላላቸው በወር 4 ሺ ብር ፤ቤተሰብ ለሌላቸው ደግሞ በወር 2 ሺ ለሶስት ወር የቤት ኪራይ የሚሆናቸውና እንዲሁም ለሁሉም ለተፈናቀሉ ዜጎች የአንድ ወር ቀለብ ወጪ በመንግስት ተሸፍኖላቸዋል፡፡
በግል ቤታቸው ይኖሩ የነበሩና ቤታቸው የተጎዳባቸው ዜጎች ቤታቸውን ለመጠገን የሚያስችል ወጪ ተሰልቶ እንዲከፈላቸውም መደረጉንም ሰምተናል፡፡