loading
በሀዋሳ የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖቻችን ከዛሬ ጀምሮ ወደ ቀያቸው ይመለሳሉ፡፡

የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት በሀዋሳ በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች ከ 1 ወር በላይ የቆዩ ተፈናቃዮች ከዛሬ ጀምሮ ወደ የቀያቸዉ ይመለሳሉ ብለዋል፡፡
አቶ ሚሊዩን ተፈናቃዮቹ የሚመለሱባቸዉ መንደሮች የቀድሞ ሰላማቸዉን ማግኘታቸዉን ተናግረዋል፡፡
ተፈናቃዮቹ እስኪቋቋሙ ድረስ ቤተሰብ ላላቸው በወር 4 ሺ ብር ፤ቤተሰብ ለሌላቸው ደግሞ በወር 2 ሺ ለሶስት ወር የቤት ኪራይ የሚሆናቸውና እንዲሁም ለሁሉም ለተፈናቀሉ ዜጎች የአንድ ወር ቀለብ ወጪ በመንግስት ተሸፍኖላቸዋል፡፡
በግል ቤታቸው ይኖሩ የነበሩና ቤታቸው የተጎዳባቸው ዜጎች ቤታቸውን ለመጠገን የሚያስችል ወጪ ተሰልቶ እንዲከፈላቸውም መደረጉንም ሰምተናል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *