AfricaHealth

የዓለም የጤና ድርጅት የዲሞክራቲክ ኮንጎ ጉዳይ አሳስቦኛል ብሏል፡፡

በሀገሪቱ የተፈጠረው አለመረጋጋት የኢቦላ ቫይረስን ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት አደጋ ላይ ጥሎታል ነው ያለው ድርጅቱ፡፡
አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ጀነራል ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም አሁን በሀገሪቱ ያለው ሁኔታ በጣም አሳሳቢ ነው ብለዋል፡፡
ዶክተር ቴዎድሮስ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ተፋላሚ ሀይሎች በአስቸኳይ ተኩስ አቁመው የጤና ባለሞያዎች እንደልባቸው ቫይረሱ ወደተከሰተበት አካባቢ ተንቀሳቅሰው ስራቸውን እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
እስካሁን 41 ሰዎች ሲሞቱ በሽተኞቹን የሚከባከቡ 7 ያህል የጤና ባለሞያዎች በቫይረሱ መያዛቸውም ታውቋል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button