ብ/ጀነራል አሳምነው ፅጌ እና ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ በላሊላ አሸንድዬ ካባ ተደረበላቸው።
አሸንድዬ፣አሸንዳ ፣ሶለል እና ሻደይ የዓለም ሀብት የሚሆኑት በባለቤትነት ስንጠብቃቸው ነው ብለዋል የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ፎዚያ አሚን። የአሸንድዬ የሴቶች በዓል “አሸንድዬ ለሰላምና አንድነት በፍቅር ለመደመር” በሚል መሪ ቃል በላሊበላ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው። በበዓሉ ላይ ብ/ጀነራል አሳምነው ፅጌ ወጣቶች ለሰላም ስሩ ሲሉ ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ ደግሞ ባህል የሚታወቀው አገር ሲኖር ነው ብለዋል ። አርትስ ቲቪ በላሊበላ ተገኝቶ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በዚህ መደሰታቸውን ተናግረዋል። በዓሉ በላሊበላ ቀጥሏል።
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a1-225x300.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a2-225x300.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a3-300x225.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a4-300x225.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a5-300x225.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a6-300x225.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a7-300x225.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a8-300x225.jpg)
![](http://www.artstv.tv/wp-content/uploads/2018/08/a9-225x300.jpg)