loading
የአሜሪካ ልዩ ሀይል ከግብጽ ጦር ጋር የጋራ ጸረ ሽብር ልምምድ ጀምሯል

አርትስ 02/13/2010
የግብጽ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ኮሎኔል ታሜር አል ሪያፊ የልምምዱ ዓላማ ከአሜሪካ ልዩ ሀይል ጋር ሞያዊ ልምድ ለመለዋወጥ ነው ብለዋል፡፡
ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው የጸረ ሽብር ልምምዱ የተጀመረው የግብጽና የአሜሪካ ጦር “ኦፕሬሽን ብራይት ስታር” የተሰኘወን ወታደራዊ ልምምድ ከመጀመራቸው 2 ቀናት ቀደም ብሎ ነው፡፡
ልምምዱ በዋናነት ሽብርተኞችን በአየርም ሆነ በምድር እንዴት መዋጋት እንደሚቻል፣ እንዲሁም የባህር ላይ ጥቃትን ያካተተ ነው ብለዋል ቃል አቀባዩ፡፡
“ኦፕሬሽን ብራይት ስታር” የተሰኘው ዋናው ወታደራዊ ልምምድ ከነገ ጀምሮ ለ12 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከአውሮፓ፣ከመካከለኛው ምስራቅና ከአፍሪካ የተውጣጡ ሀገራት ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *