loading
ፕሬዝደንት ሙላቱ በኮፊ አናን የቀብር ስነ ስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ ጋና አመሩ::

አርትስ 02/01/2011
የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በቀድሞው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ኮፊ አናን የቀብር ስነ ስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ አክራ ጋና አመሩ።
የኮፊ አናን የቀብር ስነ ስርዓት በነገው እለት የሚፈፀም ሲሆን የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና የአለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ኮፊ አናን ለአጭር ጊዜ በአጋጠማቸው ህመም ባለፈው ነሐሴ 10 / 2010 ዓ.ም በበርን ስዊዘርላንድ ህይወታቸው ማለፉ ይታወቃል።ኢቢሲ እንደዘገበዉ፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *