loading
አገሪቱ በአምቡላንስ ቁጥር የዓለም ጤና ድርጅትን መስፈርት አሟልታለች ተባለ፡፡

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር 746 አምቡላንሶችን ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለት ከተማ አስተዳደር እንዲሁም ለስምንት ዩኒቨርስቲ ሆስፒታሎች አከፋፍያለሁ ብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በቅርቡ ሌሎች 407 አምቡላንሶች ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት በመጓጓዝ ላይ ናቸው ሲል አስታውቋል፡፡ ይህም ማለት ቀደም ሲል ከተሰራጩት 1200 አምቡላንሶች ጋር ሲደመር ከሁለት ሺህ በላይ ይሆናል ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልፆ የ1859 ተጨማሪ አምቡላንሶች በግዥ በሂደት ላይ ነው ብሏል፡፡
የእነዚህ አምቡላንሶች ግዥ ከ3.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *